Skip Navigation Links    
     





 

 
የመሰረተ ልማት አውታሮችን በመዘርጋት እየተመዘገበ ያለውን ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቆመ

Monday, February 08, 2010

 
     
   

 

 አዲስ አበባ የካቲት 1/2002(ሬዲዮ ፋና) የፌዴራልና የክልል መገናኛ ዘርፍ  ተቋማት  አምስተኛ  የጋራ  የምክክር  ጉባኤ  ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተጀምሯል።

 

        የትራንስፖርትና  መገናኛ  ሚኒስትር  ዴኤታ አቶ ጌታቸው  መንግስቴ  በጉባኤው መክፈቻ  ላይ  እንደገለጡት በየአካባቢው  የመሰረተ  ልማት  አውታሮችን በማስፋፋት  የአገልግሎቱን  ጥራት  ለመጠበቅ  የሚካሄደው  ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ።

 

ባለፉት  ዓመታት  የመንገድ፣ የስልክ፣ የአየር ትራንስፖርትና  ሌሎች የመሰረተ ልማት አውታሮችን  በማስፋፋት ረገድ የተከናወኑት ሥራዎች  ስኬታማ  እንደነበሩ  ጠቅሰዋል።

 

        የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡቦንግ  በበኩላቸው መሰረተ ልማት አውታሮች ለዘላቂ  ሰላምና ልማት መረጋገጥ  የማይተካ ሚና እንዳላቸው  ተናግረዋል ።